Ministry of Planning and Development Ethiopia

Ministry of Planning and Development Ethiopia

Government Administration

About us

Website
www.pdc.gov.et
Industry
Government Administration
Company size
51-200 employees
Headquarters
Addis Ababa
Type
Government Agency

Locations

Employees at Ministry of Planning and Development Ethiopia

Updates

  • ለመላው እስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1445ኛው ኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መልካም ምኞቱን ይገልጻል። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆንም ይመኛል።

    • No alternative text description for this image
  • Ethio-Saudi Business Forum Held at Science and Technology Museum, Addis Ababa ***************************************** Addis Ababa, Ethiopia - June 5, 2024 (MoPD) Ethiopia hosted a high-profile business forum today aimed at fostering stronger investment and trade ties with Saudi Arabia. The two-day event commenced at the Science and Technology Museum in Addis Ababa. H.E. Dr. Fitsum Assefa, Ethiopia's Minister of Planning and Development, opened the forum by highlighting the longstanding ties between the two nations, which stretch back centuries. She emphasized Ethiopia's strategic location, vibrant economy, youthful population, and reformist government as key drivers for attracting Saudi investment. In her opening remarks, H.E Dr. Fitsum highlighted Ethiopia's untapped potential in various sectors, including agriculture, manufacturing, tourism, and renewable energy. She noted that Ethiopia's fertile land and favorable climate create significant potential in agribusiness, encompassing crop production, livestock rearing, and agro-processing, inviting Saudi investors to capitalize on these opportunities. The Minister also highlighted recent economic reforms undertaken by the Ethiopian government to create a more business-friendly environment. These reforms include liberalizing key sectors and implementing legal and administrative changes to reduce the cost of doing business in Ethiopia. Officials from Ethiopia’s Investment Commission and the National Bank of Ethiopia discussed the various opportunities brought about by these recent reforms. Dr. Hussein Mujib, President of the Federation of Saudi Arabian Chambers of Commerce, emphasized the historical ties between the two countries dating back to 1948. He expressed Saudi Arabia's desire to strengthen trade and investment relations not only with Ethiopia but across Africa, fostering a spirit of collaboration. Dr. Mujib noted the diverse composition of the Saudi delegation, representing various business and investment sectors, paving the way for potential partnerships with Ethiopian counterparts. A Memorandum of Understanding (MoU) was signed between the Ethiopian Chamber of Commerce and Sectoral Associations and the Federation of Saudi Arabian Chambers of Commerce, signifying a commitment to formalize collaboration. Prior to the forum, a business exhibition showcased Ethiopia's potential in various sectors, including leather, textiles, minerals, and tourism destinations. This event served to highlight the diverse investment opportunities Ethiopia offers to Saudi Arabian businesses

    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
      +4
  • Ethiopia Highlights Challenges and Commitments in Accessing Green and Climate Finance at Korea-Africa Summit ************************************************ Addis Ababa, June 4, 2024 Ethiopia participated in the High-level Forums on the sidelines of the Korea-Africa Summit 2024, which focused on the theme "Accelerating Access to Green and Climate Finance for Africa: Pioneering Korea-Africa Partnership." The forums provided a platform for mutual, beneficial, and sustainable long-term cooperative relations between Korea and Africa, facilitating partnership and new opportunities to pave the way for green growth in Africa. H.E. Dr. Nemera Gebeyehu Mamo, State Minister at the Ministry of Planning and Development, expressed Ethiopia's commitment to playing its part in the global climate agenda. He stated that Ethiopia is integrating climate resilience into its national development strategies and actively pursuing green growth pathways. "Ethiopia remains committed to creating an enabling environment for climate finance by implementing policies that promote renewable energy, sustainable agriculture, and reforestation," said H.E. Dr. Nemera. "As stated in our Nationally Determined Contribution (NDC), Ethiopia needs approximately $316 billion to achieve its climate goals by 2030, underscoring the urgent need for mobilizing substantial climate finance from diverse sources." However, Ethiopia faces several challenges in accessing green and climate finance, both domestically and internationally. Domestically, government institutions lack the capacity to present cohesive and compelling proposals to international donors and financial institutions, and there are inadequate mechanisms to monitor and report on the impacts of funded projects. The issue of debt burden also limits access to non-concessional green and climate finance.

    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
      +1
  • ባለፊት ዘጠኝ ወራት የተመዘገበው ውጤት የህዝብ ተሳትፎ በከፍተኛ ደረጃ የታየበትና ተጠቃሚነት የተረጋገጠበት እንደነበር የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ፍፁም አሰፋ ገልፀዋል፡፡ ***************************************************************************************** ግንቦት 19/2016 አዲስ አበባ (የፕ.ል.ሚ) ባለፊት ዘጠኝ ወራት ለተመዘገበው ውጤት የህዝብ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ፍፁም አሰፋ ገልፀዋል፡፡ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ፍፁም አሰፋ እንደገለፁት ባለፊት ዘጠኝ ወራት የህዝብ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር የገለፁ ሲሆን ህዝብን ተጠቃሚና አካታች ከማድረግ አኳያ በተለይ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል ፡፡ ስለ ልማት ፋይናንስ ስናስብ ቀድሞ ወደ አእምሮአችን የሚመጣው መንግስት በበጀት ወይም በትሬዠሪ መድቦ የሚሰራቸውን ስራዎች ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በብድርና ዕርዳታ በመጠቀም የሚሰሩ ናቸው ያሉት ሚኒስትሯ እንደ ሀገር ያለንን አቅም የራሳችንን ሀይል አሰባስበን ልማትን ከማሳካት አኳያ ብዙ ያልሰራንበት እንደነበር አንስተዋል። ነገር ግን ከቅርብ ግዜ ወዲህ ከገመትነውም በላይ ልማትን ለማሳካት የህዝባችንም አቅም፣ ተነሳሽነት እና ፍቃደኝት ምን ያክል እንደሆነ ያየንበት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል። ሚኒስትሯ በመግለጫቸው የአረጋውያንን ቤት ለማደስ አያንዳንዱ ዜጋ ፣ የግሉ ዘርፍ ፣ ባለሀብቶች የተለያዩ አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የሰሩት ስራ እና የሰበሰቡት አቅም ቀላል የሚባል እንዳልሆነ የገለፁ ሲሆን ሌላ ሊነሳ ሚችለው ነገር በአረንጓዴ አሻራ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ችግኝ ላይ በጀት መበጀት ሳያስፈልግ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞች በየዓመቱ መተከላቹ ነዉ ብለዋል። የህዝብ ሃይልና አቅምን በማሰባሰብ ለከፍተኛ ልማት ማዋል መጄመሩን ያነሱት ክብርት ሚኒስትር ይህም ወደፊትም በይበልጥ ተሳትፍንና ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ የሚቀጥል ስለመሆኑ ጠቁመዋል። የአፈርና ዉሃ ጥበቃ ስራ በየክልሉ ሚሊየን ዜጎች ተሳትፈው በየዓመቱ የሚሰሩ ስራ መሆኑን ያነሱት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ፤ ስራዉ  በበጀት ይሰራ ቢባል ከፍተኛ ጫና የሚፈጥር ነገር ግን በከፍተኛ ሁኔታ የህዝብን ሃይል በማሰባሰብ እየተሰራ ያለ ስራ መሆኑን ሚኒስትሯ አብራርተዋል፡፡ ትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ሌላኛው የህዝብን ተሳትፎ ያየንበት ነው ያሉት ሚኒስትሯ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ፣ተጨማሪ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት የተደረገው ንቅናቄ እንደሚታወሰው 25 ቢሊየን  የሚጠጋ ብር የፈጀ በበጀት ቢታሰብ መንግስትን የሚፈትንና በርካታ ዓመታትን ይፈጅ የነበረ ፤ ነገር ግን የህዝብ አቅም በማሰባሰብ የተሰራ ከፍተኛ ስራ ነው ብለዋል፡፡ ሌላኛው በቅርብ የጀመርነው “ጽዱ ጎዳና - ኑሮ በጤና” በሚል ንቅናቄ እንደዚሁ ፈጠራ የታከለበት ልማትን ፋይናንስ የማድረግ መንገድ ሆኖ ማህበረሰብን በማሳተፍና ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ  የሚስራ ስራ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ በአጠቃላይ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሰው ተኮር ኢንቨስትመንቶች እንደ ትምህርት ቤቶችን ማደስና መገንባት በዚህም በተለይ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ቅድመ መደበኛ  ትምህርት ቤቶች መገንባት መቻሉን፣ ከመቶ 70 ሺ በላይ የአረጋውያን እና አቅመ ደካማ ቤቶች መገንባት፣ የትምህርት ቤት ምገባ በተለይ ሌሎች የከተማ መስተዳድሮችን፣  የልማት አጋሮችን እንዲሁም በማህበረሰብ ተሳትፎ በማረጋገጥ በዚህ ዓመት 6 ነጥብ 5 ሚሊየን ተማሪዎች በላይ በትምህርት ቤት ቁርስና ምሳ መመገብ መቻሉን አመላክተዋል፡፡ በቅርብ አዲስ አበባ ተጠናቆ ወደ ስራ የገባ የአይነ ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤት በመገንባት ማንም ዜጋ ወደኃላ እንዳይቀር እየተሰሩ ያሉ ሌሎች ስራዎችንም ጨምሮ ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አኳያ በርካታ ስራዎች እንዳሉ ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡ ሚኒስትሯ አያይዘውም አጠቃላይ የመንግስት በጀትም የሚውልባቸው ዘርፎች በአብዛኛው ሰው ተኮር የሆኑ መሰረተ ልማቶችን፣ መንገዶችን ፣ የማህበራዊ ዘርፍ ልማት ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማትን በማልማት ፣የውሀ ተደራሽነትን በማስፋት ላይ አትኩሮ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች እንዳሉ አንስተዋል፡፡

    • No alternative text description for this image
  • የመካከለኛ ዘመን(2016-2018) የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ ስኬታማ እንዲሆን የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጄትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ ************************************************ ግንቦት 16/2016 ዓ.ም፣ አዳማ (የፕ.ል.ሚ) የመካከለኛ ዘመን(2016-2018) የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ ስኬታማ እንዲሆን የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጄትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ ቋሚ ኮሚቴዉ ከፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ ጋር በ2016 በጄት አመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸሙና በመካከለኛ ዘመን(2016-2018) የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ ላይ በአዳማ ሲያደርግ የነበረዉን ዉይይት አጠናቋል፡፡ በእቅዱ ላይ ገለጻ ያደረጉት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የመንግስት ኢንቨስትምንትና ፕላን መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ በረከት ተስፋጽዮን እቅዱ ያለፉትን አመታት አፈጻጸሞች ገምግሞ እና የአስር ዓመቱን የልማት እቅድ በመዳሰስ የተዘጋጄ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ማረጋገጥ ፣ ኢንቨስትመንትና የንግድ ከባቢን ማሻሻል ፣ የዘርፎችን የማምረት ምርታማነትና ተወዳዳሪነትን ማሳደግ እንዲሁም የመንግስትን የመፈጸም አቅም ማጎልበት የእቅዱ አራት ዋና ዋና ምሰሶዎች እንደሆኑ አቶ በረከት ገልጸዋል፡፡ 23 የፖሊሲ ሃሳቦችን የያዘዉ እቅዱ 133 ፕሮግራሞች እና 4 ሺህ 455 ፕሮጄክቶችን የያዘ ሲሆን 4 ነጥብ 38 ትሪሊዬን ብር ግምታዊ ኢንቨስትመንት እንደሚያስፈልገዉም ተመላክቷል፡፡ ከገለጻዉ በኋላ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጄትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ማብራሪያ ያሻቸዋል ያላቸዉን ጥያቄዎችና አስተያዬቶች ያቀረበ ሲሆን ክብርት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ እንዲሁም ሚኒስትር ዲኤታዉ ክቡር ዶ/ር ነመራ ገበዬሁ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ምክር ቤቱ ተቋማትን ሲከታተልና ሲገመግም ከመካከለኛዉ ዘመን እቅድ አንጻር እያዬ መሆን አለበት ያሉት ክቡር ዶ/ር ነመራ ገበዬሁ ፤ እቅዱ በጄትና ፋይናንስን አናቦና አስተሳሰሮ የመሄድ አዲስ ልምድን ተግባራዊ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ክብርት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ በበኩላቸዉ የመካከለኛዉ ዘመን የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ የሃገርን የመልማት አቅምና የማደግ ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ እቅዱ ሲዘጋጅ እያንዳንዱ ዘርፍ የተሳተፈበትና በፕላንና ልማት ሚኒስቴር ተጠቃሎና ተዘጋጅቶ መቅረቡን ያነሱት ክብርት ሚኒስትር በሂደቱም ብዙ አቅሞች የተፈጠሩበት መሆኑን አንስተዋል፡፡ ከተለመደዉ አስተቃቀድ ወጣ ያለና የተዘረዘረ እንዲሁም በጄትና የፋይናንስ ምንጭን ያመላከተ መሆኑን ያነሱት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ሃገራዊ የማቀድና የመፈጸም አቅምን ያሳደገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴዉ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ እና ምክትል ሰብሳቢዉ ዶ/ር አብርሃም አለማዬሁ በሰጡት ማጠቃለያ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ይህንን እቅድ በዚህ መልኩ ማዘጋጄቱ የፈጠረዉን ተቋማዊ አቅም ያሳያል ብለዋል፡፡ እቅዱ ጉጉት የፈጠረና በአግባቡ ከተፈጸመም የሚታይ ለዉጥ የሚያመጣ መሆኑን አንስተዋል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም እቅዱ ስኬታማ እንዲሆን የበኩሉን ድርሻ እንደሚያበረክት የገለጹት የቋሚ ኮሚቴዉ አመራሮች ምክር ቤቱ በተቋማት ላይ በሚያደርገዉ ክትትል ፣ ድጋፍና ቁጥጥር ላይ የመካከለኛዉን ዘመን እቅድ መሰረት ለማድረግ የሚስችል ግንዛቤ ማግኜታቸዉን አረጋግጠዋል፡፡

    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
      +8
  • የባንኮች ተቀማጭ ሂሳብ ዕድገት 2.4 ትሪሊየን መድረሱን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ አስታወቁ ****************************************************************************** ግንቦት 13/2016 አዲስ አበባ (የፕ.ል.ሚ) የባንኮች ተቀማጭ ሂሳብ ዕድገት 2.4 ትሪሊየን መድረሱን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ አስታወቁ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር በተመረጡ ሀገራዊ የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ላይ ያተኮረ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተጠቀሰው በተለይም በማክሮ ኢኮኖሚ ዘርፍ የታየው አፈፃፀም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲተያይ ከፍተኛ ዕድገት የታየበት ነዉ፡፡ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶክትር ፍፁም አሰፋ የሰጡት መግለጫ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀም ላይ ያተኮረ ሲሆን በዋናነት በማክሮ ኢኮኖሚ ዘርፍ ግብርና ለጥቅል ኢኮኖሚ ዕድገት ያለው አስተዋፆ ከፍተኛ አንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በ2016 በጄት ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 7 ነጥብ 9 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ እንደሚችል ትንበያ ተቀምጦ እንደነበር በመግለጫው አስታውሰዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በበርካታ ተግዳሮች ውስጥ ብታልፍም ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች ቆይታለች ያሉት ሚኒስትሯ ይህም የኢኮኖሚ ዕድገት በ2016 ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ትንበያ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ተቋማት ያመላከቱት ጉዳይ እንደሆነ ክብርት ሚኒስትሯ አንስተዋል፡፡ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ክብርት ዶክተር ፍፁም አሰፋ በመግለጫቸው ለጥቅል ሀገራዊ ዕድገት አስተዋፆ ከሚያደርጉ ዘርፎች መካከል ግብርና ቀዳሚው መሆኑን ገልጸዉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዋና ዋና ሰብሎች ልማት ከአምና ተመሳሳይ ግዜ ተጨማሪ ከ100 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኜቱን አንስተዋል። የስንዴ ምርት በያዘው የመሬት ሽፋን ሲቀመጥ አምና በመኽርና በበጋ መስኖ 4 ሚሊየን ሄክታር ምርት የነበረ ሲሆን በዘንድሮ ዓመት ወደ 6.5 ሚሊየን ሄክታር ከፍ ማለቱ የዘርፉን እድገት ያሳያል። ከስንዴ በተመሳሳይ በሩዝ ምርትም አምና ከ 8 ሚሊየን ኩንታል ያልበለጠ ምርት ነበር የተሰበሰበው በዘንድሮ ግን 38 ሚሊየን ኩንታል መመረቱን መረጃዎች ያሳያሉ ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡ በቡና፣ በእንሰሳት ሀብት ልማትና በሌማት ትሩፋት ፕሮጀክቶች ውስጥ ዶሮ፣ እንቁላል፣ ስጋ ፥ ወተት፣ አሳ እና ማር በማካተት የተያዩ ድጋፎችን በማድረግ የተገኙ ውጤቶችም እንዳሉ ማወቅ ተችሏል፡፡በዚህም የወተትን ምርታማነት ሲታይ አምና በተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው 2 ቢሊየን ሊትር በተጨማሪ በዚህ ዓመት ተመርቷል፡፡እንቁላልን ማየት ብንችል ደግሞ አምና ካመረትነው 1.4 ቢሊየን እንቁላል ጭማሪ ተመርቷል፡፡ ማር አምና ከተመረተው 110 ሺ ቶን በላይ ጭማሪ በዘንድሮ በዘጠኝ ወራት ማምረት መቻሉን በመግለጫው ተመላክቷል፡፡ ስለዚህ በግብርናው ዘርፍ ለጥቅል ሀገራዊ ምርት (GDP) የሚኖረው አስተዋፆ አምና ከነበረው ተጨማሪ በመኖሩ 7.9 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ይኖራልተብሎ የተቀመጠዉ ትንበያ በግብርናው በኩል የሚሳካ እንደሆነ አዝማሚያዎቹ ያሳያሉ ብለዋል የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ክብርት ዶክተር ፍፁም አሰፋ በማብራሪያቸዉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የኢንደስትሪ፣ የአምራች ዘርፍ፤ ከአምናው የተሻለ አፈፃፀም ማሳየት መቻሉን ጠቅሰዋል። 2.5 ቢሊየን ዶላር በሸቀጦች የውጭ ንግድ ገቢ የተገኘ ሲሆን ከአምናው የተቀራረበ አፈፃፀም እንደሆነም አንስተዋል፡፡ በአገልግሎት ዘርፉ በተለይ በወጪና ገቢ ንግድ፣ በትራንስፖርት፣ በቱሪዝም፣ በዲጅታል ኢኮኖሚውና በሌሎች ዘርፎች በርካታ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን፤ በትራንስፖርት ዘርፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አምና በዘጠኝ ወር ከነበረው አፈጻጸም በ25 በመቶ በላይ ማደጉን አስታውቀዋል። የዋጋ ንረቱን ወደ 23.3 በመቶ ማውረድ የተቻለ ቢሆንም በተለይ ምግብ ነክ የዋጋ ንረት 27 በመቶ በመሆኑ ሰፊ ስራን እንደሚጠይቅ አመላክተዋል፡፡ ሌላኛው ከማክሮ አፈፃፀም አኳያ የሚታየው የፋይናንስ ኢንደስትሪ ልማት ሲሆን የፋይናንስ ዘርፉ ጤናማነት የሚያመላክቱ በርካታ አማላካቾች አሉ ። ከዚ አኳያ ታዲያ የባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ ሂደት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱንና ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸርም ከፍተኛ የሆነ ዕድገት ተመዝግቧል ያሉ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት የባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ 2.4 ትሪሊየን እንደደረሰ አመላክተዋል።

    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
  • የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ንግግሮችና መልዕክቶችን የያዘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ *********************** የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ንግግሮችና መልዕክቶችን የያዘና "ከመስከረም እስከ መስከረም" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ። በመጽሐፉ ላይ የዳሰሳ ውይይት በወዳጅነት ፓርክ ተካሂዷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሪታሪያት የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመስከረም 24 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ.ም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችና ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች ላይ ያደረጓቸው 91 ንግግሮችና መልዕክቶችን ያያዘ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሪታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በውይይት መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፥ መጽሐፉ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግሮችና መልዕክቶች የያዘ 6ኛው መድብል መሆኑን ገልጸዋል። የመሪ ታሪክ የሀገር ታሪክ አካል መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ መጽሐፉ ለታሪክ አጥኚዎች፣ ለፖሊሲ አውጭዎችና ለፖለቲካ ተመራማሪዎች ግብዓት እንደሚሆን ተናግረዋል። በመድረኩ ተማሪዎች ከመጽሐፉ የተመረጡ ገጾችን እንደ ውይይት መነሻ ሃሳብ በንባብ አቅርበዋል። "ከመስከረም እስከ መስከረም" መጽሐፍ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ በእንግሊዝኛ እና በአረቢኛ ቋንቋዎች ያስተላላፏቸውን ንግግሮችና መልዕክቶች ይዟል።

    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
  • የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 7 ነጥብ 9 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ እንደሚችል አመላካች ውጤቶች  እየተመዘገቡ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ***************************************************************************************   ግንቦት 12/2016 ዓ.ም ፥ አዲስ አበባ(የፕ.ል.ሚ) የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 7 ነጥብ 9 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ እንደሚችል አመላካች ውጤቶች  እየተመዘገቡ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ገለጹ።   ክብርት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ በመንግስት የዘጠኝ ወራት የልማት አፈጻጸም ላይ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።   በማክሮ ኢኮኖሚኖሚ ፥ በመሰረተ ልማትና ፕሮጄክቶች ፥ በህዝብ ተሳትፎና አካታችነት ፥ በሃገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሞች አተገባበር እንዲሁም በአጠቃለይ የልማትና የሪፎርም ስራዎች ክትትልና ግምገማ ላይ ባተኮረዉ መግለጫ የመንግስትን የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም በተጨባጭ ማሳያዎች አብራርተዋል ክብርት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ። የማክሮ ኢኮኖሚውን በሚመለከት በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ የተመዘገቡ የምጣኔ ኃብት እድገቶች መኖራቸውን ገልጸው፤ በግብርናው ዘርፍ በሰብል ምርት ብቻ አምና በተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው የ100 ሚሊየን ኩንታል ብልጫ ተገኝቷል ብለዋል። የእንሳሳት ሀብት ልማት ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አንጻር የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል ያሉት ዶክተር ፍጹም፤ ባለፈው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወር ከተገኘው የወተት ምርት በዘንድሮው ዘጠኝ ወራት ሁለት ቢሊየን ሊትር መገኘቱን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የግብርና ዘርፉ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር መሻሻል ማሳየቱን ገልጸው፤ ይህም በ2016 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ለማስመዝገብ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት አመላካች መሆኑን አስረድተዋል። ኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም አፈጻጸም 56 በመቶ መድረሱንም ነው ሚኒስትሯ የገለጹት፡፡  የግብዓት አቅርቦት፣ የኢነርጂ አጠቃቀምና የብድር አቅርቦቱ መሻሻል አሳይቷል ብለዋል። በአገልግሎት ዘርፉ በተለይ በወጪና ገቢ ንግድ፣ በትራንስፖርት፣ በቱሪዝም፣ በዲጅታል ኢኮኖሚውና በሌሎች ዘርፎች በርካታ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን፤ በትራንስፖርት ዘርፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አምና በዘጠኝ ወር ከነበረው አፈጻጸም በ25 በመቶ ማደጉን አስታውቀዋል። የዋጋ ንረቱን ወደ 23.3 በመቶ ማውረድ የተቻለ ቢሆንም በተለይ ምግብ ነክ የዋጋ ንረት 27 በመቶ በመሆኑ ሰፊ ስራን እንደሚጠይቅ አመላክተዋል፡፡ የመንግስት ገቢና ወጪን በሚመለከት በዘንድረው ዘጠኝ ወራት 374 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ የተሰበሰበ ሲሆን ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር የ15 በመቶ ብልጫ አሳይቷል። መንግስት 495 ቢሊየን ብር ወጪ ያደረገ ሲሆን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነጻጸር ስምንት በመቶ ጨምሯል ብለዋል። ትልቁን ወጪ የሚሸፍነው የካፒታል ወጪ እንደሆነ እና ይህም 15 ነጥብ 5 በመቶ ድርሻ እንዳለው አብራርተዋል፡፡ በሌላ በኩል ከሸቀጦች የወጪ ንግድ 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር፣ ከአገልግሎት ወጪ ንግድ ደግሞ 5 ነጥብ 8 ቢሊየን ዶላር መገኘቱን ጠቁመዋል። በአጠቃላይ ለማክሮ ኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ እድገት መታየቱን ተከትሎ የ7 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ትንበያው እውን እንደሚሆን ሂደቶቹ እንደሚያሳዩ አስታዉቀዋል። የስራ አጥነት፣ የዋጋ ንረት፣ የውጭ እዳ ተጋላጭነት፣ የምርቶች ጥራትና ተወዳዳሪነትና የማክሮ ኢኮኖሚው ተግዳሮት መሆናቸውንም አመላክተዋል።

    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
  • በካርቦን ግብይት ስርዓት ግንባታ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሄደ። ************************************************ ግንቦት 6/ 2016 ዓ.ም፥አዲስ አበባ (የፕ.ል.ሚ) በካርቦን ግብይት ስርዓት ግንባታ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሄደ። በመድረኩ ላይ የአየር ንብረት ለዉጥን ለመከላከል መንግስት የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አቶ ስዩም መኮንን አስታዉቀዋል። በአሁኑ ወቅት በአየር ንብረት ለዉጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየደረሰባት የምትገኜዉ ኢትዮጵያ የተለያዩ የመከላከል ስራዎችን ብትሰራም ችግሩ አለማቀፍ ከመሆኑ አንጻር እንደ ጎርፍ ፥ ድርቅና ሌሎች መሰል አደጋዎችን እያስተናገደች ነዉ። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዲኤታዉ ክቡር አቶ ስዩም መኮንን በሃያት ሪጄንሲ ሆቴል በኢትዮጵያ ካርቦን ንግድ ማዕቀፍ ዙሪያ በተካሄደዉ ምክክር ላይ ተገኝተዉ እንደተናገሩት የአየር ንብረት ለዉጥ ጉዳይ አለምን እፈተነ ያለና በአሳሳቢነቱም ከፍተኛዉ ነዉ። በተለይ ጉዳቱ ለብክለቱ እምብዛም አስተዋጽኦ በሌላቸዉ ታዳጊ ሃገራት ላይ ክፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትር ዲኤታዉ ኢትዮጵያም የጉዳቱ ሰለባ መሆኗን አብራርተዋል። መንግስት ይህንን ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ያነሱት አቶ ስዩም ለአየር ንብረት ለዉጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት ፥ የአየር ንብረት ፖሊሲና ፕላኒንግን በአግባቡ መተግበር ፥ የመላመድና ማጣጣም ስራዎችን በትኩረት መተግበር ፥ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ እቅድ (NDC) ፥ የረዥም ጊዜ አነስተኛ የልቀት መጠንን እዉን ከማድረግ ጄምሮ የአየር ንብረት ለዉጥ ጉዳይ በ10 ዓመቱ ሃገራዊ እቅድ አንዱ ምሰሶ እንዲሆን ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ሚኒስትር ዲኤታዉ አብራርተዋል። አረንጓዴ አሻራና የሌማት ትሩፋት ስራዎችም መንግስት ያለዉን ቁርጠኝነት ያሳየባቸዉ ስራዎች መሆናቸዉን ያነሱት አቶ ስዩም የታዳሽ ሃይል ልማት ሃገሪቱ ከራሷ አልፋ ጎረቤት ሃጋራትን እያሳተፈቺበት ያለ ስራ ስለመሆኑ ገልጸዋል። የአየር ንብረት ለዉጥ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሃገራት የካርቦን ንግድን መሰለ እድልም አምጥተዋል ያሉት አቶ ስዩም ተጠቃሚ የመሆን ጅምሮች ቢኖሩም በሚፈለገዉ ደረጃ ለመሳተፍ ዘርፉን በህግ በስርአትና በማእቀፍ መምራትም ያስፈልጋል ብለዋል። ለዚህም የሚረዳ የካርቦን ግብይት ማዕቀፍም በአለም ባንክ ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል ። ከዚህ ሚገኜዉን ገቢ በማሳደግ ሃገሪቱን ተጠቃሚ ለማድረግና የአየር ንብረት ለዉጥን የመከላከሉን ስራ ዉጤታማ ለማድረግ የተጄመሩ ስራዎች ተጠናክሩ መቀጠል እንዳለባቸዉ ያነሱት አቶ ስዩም መኮንን በዚህ ረገድ የአለም ባንክ እያደረገ ያለዉን ድጋፍም አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። የአለም ባንክ የመሰረተልማት ፕሮግራም መሪ የሆኑት ዥያወፒንግ ዋንግ በበኩላቸዉ ኢትዮጵያ ከካርቦን ሽያጭ ተጠቃሚ ለመሆኑ የምትሰራዉን ስራ በማገዝ በኩል ባንኩ ድጋፉን ያጠናክራል ብለዋል። ምክክሩ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈና ሰፊ ዉይይትም የተደረገበት ነዉ።

    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
    • No alternative text description for this image
      +6

Similar pages